ስብከት ሃያ ሁሇት የቅዴሚያ ሇራሴ ክበብ

“እንዳይፈረድባችሁ አትፍረዱ፤ በምትፈርዱበት ፍርድ ይፈረድባችኋልና፥ በምትሰፍሩበትም መስፈሪያ ይሰፈርባችኋል።” ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ ያስተማረው ትምህርት አካባቢያቸውን እንዲመለከቱ፣ እነዚያን የተባረኩ ባሕርያት ከሰዎች ጋር ባላቸው ግንኙነት እንዲተገብሩ፣ ከዚያም ወደ ላይ እንዲመለከቱና ፍሬአማ ደቀ መዛሙርት እንዲሆኑ የሚያስችላቸውን መንፈሳዊ ነገሮችን እና እሴቶችን ከእግዚአብሔር ዘንድ እንዲቀበሉ ለማድረግ ነው፡፡ የዚህ ትምህርት ዓላማ የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት የሌሎችን ችግር ከመፍታታቸው በፊት የራሳቸውን ችግር መፍታት እንዳለባቸው ለማስተማር ነው፡፡